ታንዛኒያ ከኢትዮጵያ የምታስገባው የኤሌክትሪክ ኃይል ዋጋ ተመጣጣኝ ነው አለችየታንዛኒያ መንግሥት ያለበትን የኃይል እጥረት ለመቅረፍ በኬኒያ በኩል ከኢትዮጵያ ሊያስገባ ካሰበው የኤሌክትሪክ ኃይል ጋር ተያይዞ የተነሳወን ስጋት እንደተከላከለ ዘ ሲቲዝን ዘግቧል፡፡ የታንዛኒያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሉሁ ሃሳን ውሳኔው ቴክኒካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ግምቶችን ግንዛቤ ውስጥ የከተተ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ከታንዛኒያ ደቡብ ምስራቅ ክልል ወደ ሰሜን ዞን የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፍ ከፍተኛ የሆነ የኃይል ብክነት እንደፈጠረ ገልጸው፤ የሀገር ውስጥ አቅርቦት አስተማማኝ አይደለም ብለዋል።ከኢትዮጵያ የሚገባው የኤሌክትሪክ ኃይል ከአንዳንድ የሀገር ውስጥ የኃይል ማመንጫዎች ዋጋ የበለጠ ተመጣጣኝ ይሆናል ተብሎ እንደሚጠበቅ የታንዛኒያ መንግሥት ቃል አቀባይ ጌርሰን ምሲግዋ በጉዳዩ ዙርያ ባወጡት መግለጫ ተናግረዋል። "ከኢትዮጵያ በኬንያ በኩል የሚገባው የኤሌክትሪክ ኃይል ተደጋጋሚ መቆራረጦችን ለማስወገድ እና በረዥም ርቀት ማስተላለፊያ የሚደርሰውን ከፍተኛ የኃይል ብክነት ለመቀነስ ይረዳል" ሲሉ ቃል አቀባዩ አክለዋል፡፡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
ታንዛኒያ ከኢትዮጵያ የምታስገባው የኤሌክትሪክ ኃይል ዋጋ ተመጣጣኝ ነው አለች
ታንዛኒያ ከኢትዮጵያ የምታስገባው የኤሌክትሪክ ኃይል ዋጋ ተመጣጣኝ ነው አለች
Sputnik አፍሪካ
ታንዛኒያ ከኢትዮጵያ የምታስገባው የኤሌክትሪክ ኃይል ዋጋ ተመጣጣኝ ነው አለችየታንዛኒያ መንግሥት ያለበትን የኃይል እጥረት ለመቅረፍ በኬኒያ በኩል ከኢትዮጵያ ሊያስገባ ካሰበው የኤሌክትሪክ ኃይል ጋር ተያይዞ የተነሳወን ስጋት እንደተከላከለ ዘ ሲቲዝን... 11.03.2025, Sputnik አፍሪካ
2025-03-11T14:35+0300
2025-03-11T14:35+0300
2025-03-11T15:14+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2025
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий