ሩሲያ ወደ አፍሪካ የምትልከው የግብርና ምርት በ2024 የ19 በመቶ እድገት በማሳየት ከ7 ቢሊዮን ዶላር እንደተሻገረ ተገለጸ

ሰብስክራይብ
ሩሲያ ወደ አፍሪካ የምትልከው የግብርና ምርት በ2024 የ19 በመቶ እድገት በማሳየት ከ7 ቢሊዮን ዶላር እንደተሻገረ ተገለጸ የፌደራል አግሮ ኤክስፖርት ማዕከል “የሀገር ውስጥ የምግብ ምርቶች በአህጉሪቱ ለሚገኙ 45 ሀገራት ተልከዋል” ሲል ገልጿል። ግብፅ ከፍተኛ የሩሲያ የግብርና ምርቶችን በመግዛት ቀዳሚ ሀገር መሆኗን ቀጥላለች፡፡ በ2024 መገባደጃ ወደ ግብፅ የተላኩ የሩሲያ የግብርና ምርቶች የ21 በመቶ ጭማሬ አሳይተዋል።ከግብፅ በተጨማሪ አልጄሪያ፣ ሊቢያ፣ ኬንያ እና ቱኒዚያ ከአምስቱ ከፍተኛ የሩሲያ የግብርና ምርት አስመጪዎች መካከል ናቸው።አህጉሪቱ ከሩሲያ የምታስገባው የስንዴ ምርት ድርሻ በማደግ ላይ መሆኑ ተገልጿል። በ2023/2024 የምርት ዘመን ከሩሲያ አጠቃላይ የስንዴ ኤክስፖርት ውስጥ 38 በመቶውን ወደ አፍሪካ ሀገራት የላከች ሲሆን፤ በተያዘው የምርት ዘመን ይህ አሃዝ ከወዲሁ ከ50 በመቶ አልፏል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦   APK ፋይል ሊንክ  ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0