ደቡብ አፍሪካ ኤለን መስክ ስታርሊንክ በሀገሪቱ የታገደበትን ምክንያት አስመልክቶ የሰጠውን አስተያየት ውድቅ አደረገች ደቡብ አፍሪካ የተወለደው ኤለን መስክ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ በኤክስ ገፁ ላይ ባጋራው ፅሐፍ “ስታርሊንክ በደቡብ አፍሪካ ውስጥ እንዲሠራ አልተፈቀደለትም። ምክንያቱም እኔ ጥቁር አይደለሁም” ብሏል። "ይህ እውነት አይደለም፤ እውነት እንዳልሆነ አንተም ታውቃለህ። ከቆዳ ቀለም ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የለውም። የሀገሪቱን ሕጎች እስካከበረ ድረስ ስታርሊንክ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ መሥራት ይችላል" ሲሉ የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ከፍተኛ ባለስልጣን ክላይሰን ሞንዬላ ምላሽ ሰጥተዋል። የመስክ ትችት የውጭ የቴሌኮሙኒኬሽን ኦፕሬተሮች 30 በመቶ ድርሻቸው በታሪክ በተገለሉ ቡድኖች እንዲያዝ በሚያስገድደው የጥቁር ኢኮኖሚ ማብቃት ደንብ ላይ ያነጣጠረ ሳይሆን አይቀርም ነው የተባለው። ስታርሊንክ ደንቡ እንደገና እንዲሻሻል ጥያቄ አቅርቦ እንደነበርም ተገልጿል። በጉዳዩ ላይ አስተያየቱን የሰጠው የሀገሪቱ የቴሌኮም ባለስልጣን (አይካሳ) ስታርሊንክ የአገልግሎት ፈቃድ እንዳልጠየቀ አስታውቋል። በሰው ሰራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምስልበእንግሊዘኛ ያንብቡመተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
ደቡብ አፍሪካ ኤለን መስክ ስታርሊንክ በሀገሪቱ የታገደበትን ምክንያት አስመልክቶ የሰጠውን አስተያየት ውድቅ አደረገች
ደቡብ አፍሪካ ኤለን መስክ ስታርሊንክ በሀገሪቱ የታገደበትን ምክንያት አስመልክቶ የሰጠውን አስተያየት ውድቅ አደረገች
Sputnik አፍሪካ
ደቡብ አፍሪካ ኤለን መስክ ስታርሊንክ በሀገሪቱ የታገደበትን ምክንያት አስመልክቶ የሰጠውን አስተያየት ውድቅ አደረገች ደቡብ አፍሪካ የተወለደው ኤለን መስክ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ በኤክስ ገፁ ላይ ባጋራው ፅሐፍ “ስታርሊንክ በደቡብ አፍሪካ ውስጥ... 10.03.2025, Sputnik አፍሪካ
2025-03-10T15:48+0300
2025-03-10T15:48+0300
2025-03-10T16:14+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2025
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
ደቡብ አፍሪካ ኤለን መስክ ስታርሊንክ በሀገሪቱ የታገደበትን ምክንያት አስመልክቶ የሰጠውን አስተያየት ውድቅ አደረገች
15:48 10.03.2025 (የተሻሻለ: 16:14 10.03.2025)
ሰብስክራይብ