የዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ባለስልጣናት የአማፂያን መሪዎች ያሉበትን ለጠቆመ የ5 ሚሊዮን ዶላር ጉርሻ አቀረቡ "በፍርድ ወንጀለኛ የተባሉትን ኮርኒል ናንጋ፣ በርትራንድ ቢሲሚዋ እና ሱልጣኒ ማኬንጋን እስር የረዳ ማንኛውም ሰው የ5 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ያገኛል። በተጨማሪም የሸሹ ግብረ አበሮቻቸውን ፔሮት ሉዋራ፣ ኢሬንጅ ባሌንጌ እና ሌሎች በፍትሕ የሚፈለጉ ወንጀለኞች በቁጥጥር ስር ለማዋል የሚያስችል መረጃ የሰጠ የ4 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ያገኛል" ሲል የሀገሪቱ ፍትሕ ሚኒስቴር ገልጿል። ናንጋ የኮንጎ ወንዝ ጥምረት (ኤኤፍሲ) በመባል የሚታወቀው አማፂ ቡድን መሪ ነው። ባለፈው ክረምት የኮንጎ ፍርድ ቤት በጦር ወንጀል እና በሀገር ክህደት ወንጀል በሌለበት የሞት ፍርድ ፈርዶበታል። ናንጋ የኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ብሔራዊ ምርጫ ኮሚሽን ኃላፊ ሆኖ አገልግሏል። ቢሲምዋ ከኤኤፍሲ ጋር ግኑኝነት ያለውን የኤም23 ቡድን የፖለቲካ ክንፍ የሚመራ ሲሆን ማኬንጋ የኤም23 ጦር አዛዥ ነው።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
የዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ባለስልጣናት የአማፂያን መሪዎች ያሉበትን ለጠቆመ የ5 ሚሊዮን ዶላር ጉርሻ አቀረቡ
የዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ባለስልጣናት የአማፂያን መሪዎች ያሉበትን ለጠቆመ የ5 ሚሊዮን ዶላር ጉርሻ አቀረቡ
Sputnik አፍሪካ
የዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ባለስልጣናት የአማፂያን መሪዎች ያሉበትን ለጠቆመ የ5 ሚሊዮን ዶላር ጉርሻ አቀረቡ "በፍርድ ወንጀለኛ የተባሉትን ኮርኒል ናንጋ፣ በርትራንድ ቢሲሚዋ እና ሱልጣኒ ማኬንጋን እስር የረዳ ማንኛውም ሰው የ5 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ያገኛል።... 09.03.2025, Sputnik አፍሪካ
2025-03-09T17:07+0300
2025-03-09T17:07+0300
2025-03-09T17:44+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2025
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
የዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ባለስልጣናት የአማፂያን መሪዎች ያሉበትን ለጠቆመ የ5 ሚሊዮን ዶላር ጉርሻ አቀረቡ
17:07 09.03.2025 (የተሻሻለ: 17:44 09.03.2025)
ሰብስክራይብ