የኬንያ ፕሬዝዳንት እና የተቃዋሚ ፓርቲ መሪው የሥልጣን መጋራት ስምምነት ደረሱ

ሰብስክራይብ
የኬንያ ፕሬዝዳንት እና የተቃዋሚ ፓርቲ መሪው የሥልጣን መጋራት ስምምነት ደረሱ በስምምነቱ መሠረት ዊልያም ሩቶ እና ራይላ ኦዲንጋ በብሔራዊ እርቅ እና የአስተዳደር ማሻሻያዎች ላይ በትብብር ለመሥራት ቃል መግባታቸው ተነግሯል። የጠቅላይ ሚኒስትር ሚና የስምምነቱ አንድ አካል እንደሆነ ከመታወቁ ባለፈ የትብብሩ ዝርዝር አልተገለፀም። ሩቶ የስምምነቱ ዓላማ ኬንያውያንን አንድ ላይ በማሰባሰብ የሥራ እድል ፈጠራ፣ ሙስና እና የኑሮ ውድነትን የመሳሰሉ አፋጣኝ ምላሽ የሚሹ ችግሮችን መፍታት መሆኑን ተናግረዋል።  የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ለመሆን ያደረጉት ጥረት አለመሳካቱን ተከትሎ ወደ ሀገር ውስጥ ፖለቲካ የተመለሱት ኦዲንጋ፤ በመንግሥት ፖሊሲ ላይ ትልቅ ተጽእኖ ይኖራቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦   APK ፋይል ሊንክ  ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0