የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ዩክሬን ሰላምን ማረጋገጥ የሚያስችሉ እርምጃዎችን እንድትወስድ ጠየቁ

ሰብስክራይብ
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ዩክሬን ሰላምን ማረጋገጥ የሚያስችሉ እርምጃዎችን እንድትወስድ ጠየቁ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ባወጣው መግለጫ "የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ከዩክሬን ውጭ ጉዳይ ሚንስትር እንድሪ ሲቢሃ ጋር በዛሬው እለት በስልክ ተወያይተዋል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲቆም ያላቸውን ቁርጠኝነት በማስረገጥ፤ ሁሉም አካላት ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ የሚያስችሉ እርምጃዎችን እንዲወስዱ አጽንኦት ሰጥተዋል" ብሏል። ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳቸው ወቅት ቢሮ በገቡ በ24 ሰዓታት ውስጥ በዩክሬን ያለውን ጦርነት እንደሚያስቆሙ ቃል ገብተው ነበር። በዩክሬን የአሜሪካ ልዩ ልዑክ ኪዝ ኬሎግ በበኩላቸው ከጥር 12ቱ የትራምፕ በዓለ ሲመት ጀምሮ ባሉት 100 ቀናት ውስጥ ግጭቱን የማስቆም ግብ አስቀምጠዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦   APK ፋይል ሊንክ  ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0