ኢትዮጵያ ከሩሲያ ጋር በሚኖራት የኒውክሌር ኃይል ትብብር "ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት" ማስመዝገብ ትችላለች ተባለ

ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ከሩሲያ ጋር በሚኖራት የኒውክሌር ኃይል ትብብር "ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት" ማስመዝገብ ትችላለች ተባለ በሩሲያዊ ብሔራዊ ኮርፖሬሽን "ሮሳቶም"፣ በሞስኮ የኢንጂነሪግ ፊዚክስ ኢንስቲትዩት እና ዓለም አቀፍ የምርምር እና የትምህርት ማዕከል "ኦብኒስክ ቴክ" አማካኝነት የተዘጋጀው የቴክኖሎጂና ትምህርት ፎረም በአዲስ አበባ ከተማ ተካሂዷል። የሩሲያ አቶሚክ ኃይል ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር ታትይና ኦሲፖቫ በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ ከሩሲያ ጋር በሚኖራት የኒውክሌር ኃይል ትብብር "ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት" ማስመዝገብ ትችላለች ብለዋል። በአፍሪካ የሩሲያ ኒውክሌር ትምህርት ፕሮግራም አስተባባሪ ማሳምባ ካህ፤ አፍሪካ በስልጠና ረገድ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋት እና ከሩሲያ ጋር ያለው ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ለስፑትኒክ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።በኢትዮጵያ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ በቴክኖሎጂና ኢነርጂ ዘርፍ አበረታች ለውጦች እያታዩ ነው ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ ኒውክሌር ኢነርጂ ሶሳይቲ ፕሬዝዳንት እምሻው ዳምጠው ናቸው። ሀገሪቱ በዘርፉ ከሩሲያ ጋር በትብብር እየሰራች እንደሆነም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በቴክኖሎጂው ዘርፍ በተለይም በሰው ሰራሽ አስተውህሎትና በኒውክሌር ኢነርጂ ልማት ትብብራቸውን ያጠናክራሉም ተብሏል። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦   APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0