ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለኮንግረስ ባደረጉት ንግግር ያነሷቸው ቁልፍ ነጥቦች፡-

ሰብስክራይብ
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለኮንግረስ ባደረጉት ንግግር ያነሷቸው ቁልፍ ነጥቦች፡- ዘለንስኪ በተቻለ ፍጥነት ለድርድር መቀመጥ እንደሚፈልጉ የሚገልጽ ደብዳቤ እንደላኩላቸው ገልጸዋል። ሩሲያ ለሰላም ድርድር መዘጋጀቷን የሚጠቁሙ "ጠንካራ ምልክቶች" አሉ ብለዋል። የዩክሬንን ግጭት በተመለከተ "እብደቱ መቆም" አለበት በማለት ንግግር እንዲጀመር አሳስበዋል። ዩናይትድ ስቴትስ ሕዝቦቿ ከፈቀዱ ግሪንላንድን ወደ ግዛቷ ለመቀበል ፈቃደኛ እንደሆነችና ድሴቷን "በአንድ ወይም በሌላ መንገድ" የራሏ እንደምታደርግ ተናግረዋል፡፡ ከአሜሪካ ኩባንያ ጋር ስምምነት ከተደረገ በኋላ ዩናይትድ ስቴትስ የፓናማ ካናልን ዳግም ትቆጣጠራለች ብለዋል፡፡ ዋሽንግተን ወደ ሀገር ውስጥ በሚገቡ እቃዎች ላይ የቀረጥ ጭማሪ ታደርጋለች። ቻይና፣ ህንድ እና የአውሮፓ ሕብረት ከመጋቢት 24 ጀምሮ አጸፋዊ ቀረጥ ይጣልባቸዋል፡፡ ኮንግረስ ሙሉ በሙሉ በዩናይትድ ስቴትስ ለሚመረተው የላቀ የሚሳኤል መከላከያ ስርዓት “ጎለደን ዶም” የገንዘብ ድጋፍ እንዲመድብ ጠይቀዋል። የባለሙያዎች ቅጥር ሙያዊ ብቃትን መሠርት ያደረግ እንጂ ዘር እና ጾታን ተገን ያደረገ መሆን የለበትም ብለዋል። ዩናይትድ ስቴትስ ማርስ ላይ "እና ከዛም ባሻገር" ባንዲራዋን ትተክላለች። ትራምፕ ለአሜሪካ "ዓለም ከዚህ በፊት አይቶት የማያውቅ" "ወርቃማ ዘመን" ቃል ገብተዋል፡፡በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦   APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0