ሩሲያ ለኢትዮጵያ ተማሪዎች የምትሰጠውን የነጻ ትምህርት እድል አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ ይህ የተገለፀው በሩሲያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ገነት ተሾመ ከሩሲያ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ምክትል ሚኒስትር ሞጊሌቭስኪ ኮንስታንቲን ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት ነው። የሩሲያው ባለስልጣን የሁለቱ ሀገራት የትምህርት ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና እና ሩሲያ ለኢትዮጵያ ተማሪዎች የምትሰጠውን ነጻ የትምህርት እድል እየጨመረች እንደምትመጣ በውይይቱ ላይ አስታውቀዋል። ሚኒስትሩ የሩሲያ ፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ቫለንቲና ማትቪዬንኮ በቅርቡ በኢትዮጵያ ባደረጉት የሥራ ጉብኝት፤ የሁለቱን ሀገራት የትምህርት ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት መንገድ ዙርያ ከኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ አመራሮች ጋር መምከራቸውን ገልጸዋል።አምባሳደር ገነት ሩሲያ ለኢትዮጵያ ተማሪዎች ለምትሰጠው የትምህርት እድል ምስጋና አቅርበው፤ ሀገራቱ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ እና በማህበራዊ ጉዳዮች ትብብራቸው እያደገ መምጣቱን ጠቁመዋል ሲል በሞስኮ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
ሩሲያ ለኢትዮጵያ ተማሪዎች የምትሰጠውን የነጻ ትምህርት እድል አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ
ሩሲያ ለኢትዮጵያ ተማሪዎች የምትሰጠውን የነጻ ትምህርት እድል አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ
Sputnik አፍሪካ
ሩሲያ ለኢትዮጵያ ተማሪዎች የምትሰጠውን የነጻ ትምህርት እድል አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ ይህ የተገለፀው በሩሲያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ገነት ተሾመ ከሩሲያ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ምክትል ሚኒስትር ሞጊሌቭስኪ ኮንስታንቲን ጋር ውይይት... 01.03.2025, Sputnik አፍሪካ
2025-03-01T15:45+0300
2025-03-01T15:45+0300
2025-03-01T16:14+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2025
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
ሩሲያ ለኢትዮጵያ ተማሪዎች የምትሰጠውን የነጻ ትምህርት እድል አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ
15:45 01.03.2025 (የተሻሻለ: 16:14 01.03.2025)
ሰብስክራይብ