አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የማንነት መገለጫ አትላስ ሊያዘጋጅ ነው

ሰብስክራይብ
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የማንነት መገለጫ አትላስ ሊያዘጋጅ ነውአንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያን ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የማንነት መገለጫ አትላስ (የኢትኖግራፊክና የቋንቋ ባህርያት) ፕሮፋይል ለማዘጋጀት የሚያስችለውን ስምምነት ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር እና ከፌዴሬሽን ምክር ቤት ጋር ተፈራርሟል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ በፊረማ ሥነ ሥርዓቱ ላይ እንዳሉት፤ የሚዘጋጀው አትላስ የኢትዮጵያን ብሔረሰቦች የቋንቋ ብዛትና ስብጥር በጥናት ለማረጋገጥ ብሎም ትክክለኛ ቁጥራቸውን ለማወቅና በተገቢው መልኩ እንዲከበሩ ያስችላል ሲሉ አብራርተዋል።የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘው ተሻገር በበኩላቸው አትላሱ በኢትዮጵያውያን መካከል ያለውን የዘመናት አብሮነት በማጎልበት ረገድ ሚናው የጎላ እንደሚሆን ጠቅሰው፤ ተግባራዊነቱን እውን ለማድረግ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የበኩሉን እገዛ እንደሚያደርግ ገልጸዋል። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦   APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0