ኒጀር በውትድርና እና በፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ የኢትዮጵያን ድጋፍ እንደምትፈልግ ገለፀች

ሰብስክራይብ
ኒጀር በውትድርና እና በፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ የኢትዮጵያን ድጋፍ እንደምትፈልግ ገለፀች የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስትር ኢንጅነር አይሻ መሐመድ በኒጀር ሪፐብሊክ አቻቸው ሌተናል ጀኔራል ሳሊፎ ሞዲ የተመራውን ወታደራዊ ልዑክ በዛሬው እለት ተቀብለው አነጋግረዋል። የሁለቱ ሀገራት የጦር አመራሮች በውይይታቸው ወቅት በርካታ ወታደራዊ እና ሀገራዊ ጉዳዮችን እንዳነሱ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አስታውቋል። የኒጀር መከላከያ ሚኒስትር ሀገራቸው በውትድርና እና በፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ የኢትዮጵያን ድጋፍ እንደምትፈልግ እና በጋራ ለመስራትም ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ አክለውም የኢትዮጵያን ሠራዊት ልምድ እና የወታደራዊ ትምህርት ቤቶችን ተሞክሮ በመቅሰም፤ ኒጀርን ታላቅ የሚያስብል ዘመናዊ የውትድርና ተቋም መገንባት እንደሚችሉ እርግጠኛ መሆናቸውን ገልፀዋል ሲል የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስቴር በማህበራዊ የትስስር ገፁ አስታውቋል፡፡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦   APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0