የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ የምስራቅ ኮንጎን የሰላም ሂደት እንዲያስተባብሩ ተመረጡ

ሰብስክራይብ
የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ የምስራቅ ኮንጎን የሰላም ሂደት እንዲያስተባብሩ ተመረጡ በኤሜ23 እና በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መካከል የሚደረገውን ጦርነት ለማስቆም የደቡብ አፍሪካ ልማት ማህበረሰብ (ሳድክ) እና የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ (ኢኤሲ) በቅርቡ በታንዛኒያ ዳሬ ሰላም ባደረጉት ስብሰባ፤ የቀድሞዎቹ የኬንያ እና የናይጄሪያ ፕሬዝዳንቶች ኡሁሩ ኬንያታ እና ኦሊሴጎን ኦባሳንጆ፤ ከቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ጋር የሰላም ሂደቱን እንዲያስተባብሩ ተመርጠዋል።ሁለቱ ተቋማት በጋራ ባወጡት መግለጫ ሁሉም ወገኖች በኢኤሲ እና ሳድክ የመሪዎች ጉባኤ ወቅት ይፋ የተደረገውን የተኩስ አቁም እንዲያከብሩ አሳስበዋል። በተጨማሪም ኤም23 እና ሌሎች ተዋናዮች በምስራቅ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሚያደርጉትን ተጨማሪ ግስጋሴ በአፋጣኝ እንዲያቆሙ እና የተኩስ አቁም ስምምነቱን እንዲያከብሩ ጠይቀዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦   APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0