ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ለሚቀጥሉት አራት ወራት የኮባልት ማዕድን ወደ ውጭ እንዳይላክ አገደች ሀገሪቱ እርምጃውን የወሰደችው በዓለም ገበያ ያለውን ከፍተኛ የኮባልት ምርት አቅርቦት ለመቆጣጠር ነው። ከፍተኛ የሆነው የኮባልት አቅርቦት የምርቱ ዋጋ ያለማቋረጥ እንዲያሽቆልቆል ማድረጉ ተገልጿል። ውሳኔው "በማዕድኑ መነሻ እና የአቅርቦት ሰንሰለት ላይ ያለውን ቁጥጥር የማጠናከር እና ማዕድኑ በአካባቢው አቅም እንዲወጣ የማበረታታት" ዓላማ አለው ሲል የሀገሪቱ የማዕድን ሚኒስቴር አስታውቋል። ይህ የእገዳ ውሳኔ በሶስት ወራት ውስጥ ሊገመገም እንደሚችል ኤጀንሲው ጠቁሟል። የመኪና ባትሪን ጨምሮ በተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ መገልገያዎች ውስጥ ጥቅም ላይ የሚውለውን የኮባልት ማዕድን ሶስት አራተኛ ለዓለም የምታቀርበው ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ናት። እገዳው ከጥር ወር ጀምሮ እንደ አዲስ ከተቀሰቀሰው የምስራቅ ኮንጎ ግጭት በኋላ የመጣ ነው። ከጥር ወር ጀምሮ አብዛኞቹ ሲቪሎች የሆኑ ከ7 ሺህ በላይ ሰዎች ህይወታቸውን እንዳጡ ጠቅላይ ሚኒስትር ጁዲት ሱሚንዋ ቱሉካ በትላንትናው እለት በጄኔቫ ተናግረዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ለሚቀጥሉት አራት ወራት የኮባልት ማዕድን ወደ ውጭ እንዳይላክ አገደች
ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ለሚቀጥሉት አራት ወራት የኮባልት ማዕድን ወደ ውጭ እንዳይላክ አገደች
Sputnik አፍሪካ
ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ለሚቀጥሉት አራት ወራት የኮባልት ማዕድን ወደ ውጭ እንዳይላክ አገደች ሀገሪቱ እርምጃውን የወሰደችው በዓለም ገበያ ያለውን ከፍተኛ የኮባልት ምርት አቅርቦት ለመቆጣጠር ነው። ከፍተኛ የሆነው የኮባልት አቅርቦት የምርቱ ዋጋ... 25.02.2025, Sputnik አፍሪካ
2025-02-25T18:13+0300
2025-02-25T18:13+0300
2025-02-25T18:44+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2025
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ለሚቀጥሉት አራት ወራት የኮባልት ማዕድን ወደ ውጭ እንዳይላክ አገደች
18:13 25.02.2025 (የተሻሻለ: 18:44 25.02.2025)
ሰብስክራይብ