የሴኔጋል መንግሥት እና አማፂው የካሣሞንስ ዲሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ የሰላም ስምምነት ተፈራረሙ

ሰብስክራይብ
የሴኔጋል መንግሥት እና አማፂው የካሣሞንስ ዲሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ የሰላም ስምምነት ተፈራረሙ በጊኒ ቢሳው ፕሬዝዳንት ኡማሮ ሲሶኮ ኢምባሎ አሸማጋይነት እሁድ እለት በጊኒ ቢሳው ቤተ-መንግሥት የተፈረመው ስምምነት፤ ለአራት አስርት ዓመታት ለዘለቀው ግጭት መቋጫ ያስገኘ እንደሆነ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። የሴኔጋሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ኡስማኔ ሶንኮ፤ የሴኔጋል መንግሥትን እና የካሣሞንስ ዲሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄን (ኤምኤፍዲሲ) በማሸማገል ለተጫወቱት ሚና የጊኒ ቢሳውን ፕሬዝዳንት አመስግነዋል። ከሰሜን ሴኔጋል በጋምቢያ የተነጠለችው ካሣሞንስ፤ ከጎርጎሮሳውያኑ 1982 ጀምሮ የግጭት መናኸሪያ ሆና፤ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች እንደሞቱ እና የአካባቢው ኢኮኖሚ እንደተጎዳ ተገልጿል። ኤምኤፍዲሲ ከተመሠረተበት 1982 ጀምሮ ለነፃነት ሲታገል ቆይቷል። በትንሹ 250 የሚሆኑ የንቅናቄው ተዋጊዎች በቀድሞዋ የተገንጣዮች ዋንኛ ይዞታ ሞንጎኔ በግንቦት 2023 የጦር መሳሪያቸውን አስረክበዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0