የሱዳን ጦር በደቡብ ሱዳን የምትገኘውን አልኮቴን ከተማ ከፈጥኖ ደራሽ ኃይል አስለቀቀ

ሰብስክራይብ
የሱዳን ጦር በደቡብ ሱዳን የምትገኘውን አልኮቴን ከተማ ከፈጥኖ ደራሽ ኃይል አስለቀቀ የፈጥኖ ደራሽ ኃይል በኋይት ናይል ግዛት ውስጥ ከምትገኘው የአልኮቴን ከተማ ለቆ እንደወጣ፤ የአካባቢውን የበጎ ፈቃደኞች ቡድን ጠቅሰው መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ከካርቱም በስተደቡብ 100 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምተገኘው አልኮቴን ከተማ፤ ደቡብ ሱዳን ውስጥ በፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ቁጥጥር ስር የቆየች ብቸኛ ከተማ ነበረች። የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል በዳርፉር ከሚገኙት አምስት ግዛቶች አሁን ላይ አራቱን ተቆጣጥሮ የሚገኝ ሲሆን፤ ሰሜን እና ምስራቅ ሱዳን ግን በአብዛኛው ግጭቱ ያልደረሰባቸው አካባቢዎች ናቸው። የሱዳን ጦር በሰሜን የካርቱም ግዛት የምትገኘውን ባሪ ከተማ 90 በመቶ፣ የምዕራብ ኦምዱርማን አብዛኛውን አካባቢ እና ቁልፍ ቦታዎችን ጨምሮ ማዕከላዊ ካርቱምን 60 በመቶ ተቆጣጥሮ ይገኛል። እንደ መገናኛ ብዙሃኑ ዘገባ ከሆነ፤ የሱዳን ጦር እነዚህን ስትራቴጂካዊ ስፍራዎች ለመክበብ የተቃረበ ሲሆን፤ የፈጥኖ ደራሽ ኃይል ተዋጊዎች በበኩላቸው በምስራቃዊ እና በደቡባዊ መንደሮች ውስጥ ይገኛሉ።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0