አፍሪካ የምግብ ዋስትናዋን ለማረጋገጥ ከሩሲያ ጋር ያልተገደበ የእህል እና የማዳበሪያ ንግድ እንዲኖራት ትፈልጋለች ተባለ አፍሪካ ሩሲያን ጨምሮ ከእህል እና ከመዳበሪያ አቅራቢዎች ጋር ተደራድሮ የመግዛት ፍፁም ነፃነት እንዲኖራት ትፈልጋለች፤ ሲሉ የብራዛቪል ፋውንዴሽን ፕሬዝዳንት ዣን-ኢቭ ኦሊቪዬር ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ ይህን ያሉት የቡድን 20 ሀገራት ሊቀመንበር ደቡብ አፍሪካ፤ ቀዳሚ የእህል እና ማዳበሪያ ላኪ ሀገር በሆነችው ሩሲያ ላይ ማዕቀብ ተጥሎ ባለበት በዚህ ወቅት፤ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ቅድሚያ የምትሰጠው ጉዳይ እንደሆነ መግለጿን ተከትሎ ነው። "ችግሩ የአሜሪካ ማእቀብ ትኩረቱን በዋናነት በሩሲያ የእህል ምርቶች ላይ ማድረጉ ነው፤ ሆኖም ማዳበሪያንም ማንሳት አለብን። የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ማዳበሪያ ወሳኝ ነው። ሩሲያ የማዳበሪያ ምርትን በማቅረብ ረገድ ሚናዋ ከፍተኛ መሆኑን በደንብ የምናውቀው ጉዳይ ነው" ሲሉ የፋውንዴሽኑ ፕሬዝዳንት ተናግረዋል። በመሆኑም የአፍሪካ ሀገራት የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ ከሩሲያ ጋር ለመገበያየት ፍላጎት አላቸው ሲሉም አክለዋል። "ይህ የደቡብ አፍሪካ ብቻ አቋም ሳይሆን በአጠቃላይ የአፍሪካ የጋራ አቋም ነው" ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
አፍሪካ የምግብ ዋስትናዋን ለማረጋገጥ ከሩሲያ ጋር ያልተገደበ የእህል እና የማዳበሪያ ንግድ እንዲኖራት ትፈልጋለች ተባለ
አፍሪካ የምግብ ዋስትናዋን ለማረጋገጥ ከሩሲያ ጋር ያልተገደበ የእህል እና የማዳበሪያ ንግድ እንዲኖራት ትፈልጋለች ተባለ
Sputnik አፍሪካ
አፍሪካ የምግብ ዋስትናዋን ለማረጋገጥ ከሩሲያ ጋር ያልተገደበ የእህል እና የማዳበሪያ ንግድ እንዲኖራት ትፈልጋለች ተባለ አፍሪካ ሩሲያን ጨምሮ ከእህል እና ከመዳበሪያ አቅራቢዎች ጋር ተደራድሮ የመግዛት ፍፁም ነፃነት እንዲኖራት ትፈልጋለች፤ ሲሉ... 23.02.2025, Sputnik አፍሪካ
2025-02-23T14:39+0300
2025-02-23T14:39+0300
2025-02-23T15:04+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2025
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
አፍሪካ የምግብ ዋስትናዋን ለማረጋገጥ ከሩሲያ ጋር ያልተገደበ የእህል እና የማዳበሪያ ንግድ እንዲኖራት ትፈልጋለች ተባለ
14:39 23.02.2025 (የተሻሻለ: 15:04 23.02.2025)
ሰብስክራይብ