የፀጥታው ምክር ቤት ሩዋንዳ ወታደሮቿን ከኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እንድታሰወጣ ጠየቀ

ሰብስክራይብ
የፀጥታው ምክር ቤት ሩዋንዳ ወታደሮቿን ከኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እንድታሰወጣ ጠየቀ የምክር ቤቱ 15 አባላት የውሳኔ ሀሳቡን በሙሉ ድምፅ የደገፉት ሲሆን፤ "የሩዋንዳ መከላከያ ኃይል ለኤም23 የሚያደርገውን ድጋፍ በአስቸኳይ እንዲያቆም እና ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ከኮንጎ ግዛት ለቆ እንዲወጣ" በማሳሰብ፤ ኤም23 የሚያካሂደውን ጥቃት እና ግስጋሴ አውገዘዋል። በፈረንሳይ የቀረበው የውሳኔ ሀሳብ ኮንጎ እና ሩዋንዳ ያለ ምንም ቅደመ ሁኔታ ወደ ዲፕሎማሲያዊ ድርድር እንዲመለሱ ይጠይቃል። በተመድ የሩሲያ አምባሳደር ቫሲሊ ኔቤንዚያ የውሳኔ ሀሳቡ በተመድ ውስጥ እና በአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ወቅት የተደረገ የዲፕሎማሲ ጥረት ውጤት ነው ብለዋል። "ይህ የውሳኔ ሀሳብ ያለ ምንም መዘግየት በሁሉም አካላት ተግባራዊ መሆን አለበት። ግጭቱ በአስቸኳይ መቆም አለበት። የሰዎች ህይወት መዳን አለበት። ሲቪሉ ሕዝብ ወደ ቀዬው መመለስ አለበት" ሲሉ ኔቤንዘያ አፅንኦት ሰጥተዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0