በኢትዮጵያ የተመረተ አዲስና ዘመናዊ ፓስፖርት ይፋ ሆነ

ሰብስክራይብ
በኢትዮጵያ የተመረተ አዲስና ዘመናዊ ፓስፖርት ይፋ ሆነ ዘመኑ አሁን የደረሰበትን ቴክኖሎጂ በመጠቀም በኢትዮጵያ ውስጥ ተመርቷል የተባለው አዲስ ፓስፖርት፤ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በተገኙበት በዛሬው እለት ይፋ ሆኗል። ፕሬዝዳንቱ በዚህ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ የኤሌክትሮኒክ ፓስፖርቱ ለዜጎች የተሰጠውን ዋጋ የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡ ሰነዱ የፓስፖርት ባለቤቱን መረጃና የጣት ዐሻራ የያዘ የኤሌክትሮኒክስ ቺፕስ አለው ሲል የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አስታውቋል። የፓስፖርቱ የቪዛ ገጾች የኢትዮጵያን መልክ የያዙ መሆናቸውም ተጠቅሷል። ፓስፖርቱ በሀገር ውስጥ መመረት መቻሉ ከዚህ በፊት ይወጣ የነበረው የውጭ ምንዛሪ እንዲቀር ያደርጋልም ተብሏል። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0