ኢትዮጵያና ሶማሊያ የመጀመሪያ ዙር የቴክኒክ ውይይታቸውን በትናትናው እለት በአንካራ አካሄዱ

ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያና ሶማሊያ የመጀመሪያ ዙር የቴክኒክ ውይይታቸውን በትናትናው እለት በአንካራ አካሄዱ የቱርክ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሀካን ፊዳን ከኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር የተናጠል ውይይት እንዳካሄዱ አናዶሉ ኤጄንሲ ነው የዘገበው። የመጀመሪያው ዙር የቴክኒክ ውይይት በመልካም መንፈስ የተካሄደ እንደነበርም ዘገባው ጨምሮ ገልጿል።ሁለቱ አካላት ቀጣዩ ዙር የቴክኒክ ድርድር በቱርክ አመቻችነት በመጋቢት ወር እንዲካሄድ ስምምነት ላይ ደርሰዋል።የቴክኒክ ውይይቱ በቱርክ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ታይፕ ኤርዶዋን አደራዳሪነት፤ በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና በሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሺክ ሞሐሙድ መካከል የተደረሰው የአንካራ ስምምነት አካል ነው። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0