የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ከበርካታ ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በሩሲያ እና የአሜሪካ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን መካከል ከተደረገው ውይይት በኋላ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የተነሱ ቁልፍ ነጥቦች፦ 🟠 ከአሜሪካ ተወካዮች ጋር በጣም ጠቃሚ ውይይት ተደርጓል። 🟠 አሜሪካ ለሞስኮ አቋም የበለጠ ትኩረት መስጠት እንደጀመረች የሚያሳምን በቂ ምክንያት አለ። 🟠 ሩሲያ እና አሜሪካ በጂኦፖለቲካ ዘርፎች እና በኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ጥረቶችን ለማስተባበር ሁሉም ነገር መደረግ እንዳለበት ተስማምተዋል። 🟠 ሞስኮ እና ዋሽንግተን በኤምባሲዎቻቸው ስራ ላይ ያሉ ችግሮችን በቅርብ ጊዜ ውስጥ ለማስወገድ ተስማምተዋል። 🟠 ሩሲያ እና አሜሪካ በሞስኮ እና በዋሽንግተን አምባሳደሮችን ለመሾም ተስማምተዋል። 🟠 የዩክሬንን ግጭት የመፍታት ሂደት በቅርብ ጊዜ ውስጥ እንዲጀመር እና ተደራዳሪዎችን ለመሾም ከስምምነት ላይ ተደርሷል። 🟠 የሩሲያ እና አሜሪካ ተደራዳሪዎች ከተሾሙ በኋላ በሁለቱ ወገኖች መካከል መደበኛ የሆነ ምክክር ይጀመራል።🟠 የሩሲያ ልዑካን ቡድን የኔቶ ወታደሮች በዩክሬን መገኘት ተቀባይነት እንደሌለው ለአሜሪካው ልዑክ አስረድተዋል። 🟠 የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የኢኮኖሚ ትብብር ላይ እንቅፋት የሆኑ ችግሮችን ማስወገድ እንደሚያስፈልግ ተስማምተዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ከበርካታ ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በሩሲያ እና የአሜሪካ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን መካከል ከተደረገው ውይይት በኋላ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የተነሱ ቁልፍ ነጥቦች፦
17:53 18.02.2025 (የተሻሻለ: 18:04 18.02.2025)
ሰብስክራይብ