የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዳሚትሪ ፔስኮቭ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የሰጡት መግለጫ፦

ሰብስክራይብ
የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዳሚትሪ ፔስኮቭ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የሰጡት መግለጫ፦ 🟠 ፑቲን አስፈላጊ ከሆነ ከዘለንስኪ ጋር ለመደራደር ዝግጁ ቢሆኑም ህጋዊነታቸው ላይ የሚነሱ ጉዳዮች ግምት ውስጥ መግባት አለበት የሚል አቋም አላቸው። 🟠 ሩሲያ ከአውሮፓ እና ከቀድሞ የአሜሪካ አስተዳደር በተቃራኒው በዩክሬን ያለው ግጭት በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ ትሻለች። 🟠 በዩክሬን ጉዳይ የሩሲያ ዋና ትኩረት ቢቻል በሰላማዊ መንገድ ግቦቿን ማሳካት ነው። 🟠 ፑቲን እና ትራምፕ ሊገናኙ የሚችሉበት ቀን በሪያድ የልዑካን ቡድን ስብሰባ ላይ ሊታወቅ ይችላል። 🟠 የአውሮፓ ሕብረት ወታደራዊ ስብስብ ስላልሆነ የዩክሬን ሕብረቱን መቀላቀል የኪዬቭ ሉዓላዊ መብት ነው። 🟠 የአውሮፓ ሕብረት ጦር ምስረታን አስመልክቶ የተሰጡ መግለጫዎች ጥብቅ ክትትል ያስፈልጋቸዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0