የሩሲያ እና አሜሪካን ግኑኝነት ወደ ነበረበት ለመመለስ እና የዩክሬንን ጉዳይ ለመፍታት የሚካሄደው ንግግር ቀጥሏል

ሰብስክራይብ
የሩሲያ እና አሜሪካን ግኑኝነት ወደ ነበረበት ለመመለስ እና የዩክሬንን ጉዳይ ለመፍታት የሚካሄደው ንግግር ቀጥሏል እስካሁን የታወቁ ጉዳዮች፦ 🟠 ስብሰባው ለመገናኛ ብዙሃን ቅድመ መግለጫ በመስጠት ተጀምሯል። 🟠 በሩሲያ በኩል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ እና የሩሲያ ፕሬዝዳንት አማካሪ ዩሪ ኡሻኮቭ በድርድሩ ላይ ተገኝተዋል። 🟠 በአሜሪካ በኩል የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሚካኤል ዋልትዝ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ እና የመካከለኛው ምስራቅ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ተገኝተዋል። 🟠 ከአሜሪካ ጋር የሚደረገው የኢኮኖሚ ድርድር ከ2 እስከ 3 ወራት መሻሻሎችን ሊያመጣ ይችላል ሲሉ በመካሄድ ላይ ያለውን ድርድር የኢኮኖሚ ክፍል የሚመሩት የሩሲያ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ፈንድ ኃላፊ ኪሪል ዲሚትሪቭ ገልጸዋል። 🟠 በድርድሩ ወቅት የሩሲያ ተሳታፊዎች የአሜሪካ ባልደረቦቻቸውን ያዳምጣሉ የተባለ ሲሆን በቀጣይ እርምጃዎች ዙርያ ፑቲን እና ትራምፕ ውሳኔ እንደሚሰጡ ይጠበቃል። ውይይቱ የሳዑዲ ባለስልጣናት ልዑካንን እና የውጭ ሀገር እንግዶችን ለመጋበዝ በሚመርጡት አድ-ዲሪያ ቤተ-መንግሥት በመካሄድ ላይ ይገኛል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0