የጋዛ መልሶ ግንባታ እቅድ ፍልስጤማውያን፣ የአረብ ሀገራት እና ዓለም አቀፉን ማህበረስብ በማሳተፍ እየተዘጋጀ ነው ስትል ግብፅ ገለፀች

ሰብስክራይብ
የጋዛ መልሶ ግንባታ እቅድ ፍልስጤማውያን፣ የአረብ ሀገራት እና ዓለም አቀፉን ማህበረስብ በማሳተፍ እየተዘጋጀ ነው ስትል ግብፅ ገለፀችየግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ፤ በዳሬል ኢሳ ከተመራ የዩናይትድ ስቴትስ ኮንግረስ ልዑክ ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት እንደተናገሩት፤ ግብፅ ጋዛን መልሶ ለመገንባታ ሁሉን አቀፍ ባለብዙ ደረጃ እቅድ እያዘጋጀች ትገኛለች። ሚኒስትሩ የእስራኤል-ፍልስጤም ግጭት የፖለቲካ መፍትሄ እንደሚያሻው ያስረዱ ሲሆን፤ የሁለት ሀገራት መፍትሄን መሰረት ያደረገ የተዋሃደች የፍልስጤም ሀገር ምሥረታን አጥብቀው እንደሚደግፉ ገልፀዋል። ሚኒስትሩ በጋዛ ያለውን አስከፊ የሰብዓዊ ሁኔታ አጽንኦት በመስጠት፤ ቀጣይነት ያለው እና የተቀላጠፈ የሰብዓዊ ድጋፍ እንዲደረግም ጥሪ አቅርበዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0