የኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር "የሩዋንዳ ወታደሮች" ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ አሳሰቡ

ሰብስክራይብ
የኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር "የሩዋንዳ ወታደሮች" ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ አሳሰቡ "እኛ ነፃ ሀገር ነን፤ እናም የግዛት አንድነታችንን መጠበቅ አለብን" ሲሉ ጁዱት ሱሚንዋ ለምዕራባውያን ሚዲያ ተናግረዋል። ሩዋንዳ ጦሯ ኤም23 አማፂያንን ይደግፋል መባሉን የምታስተባብል ሲሆን፤ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሪፖርት ግን 4 ሺህ የሩዋንዳ ወታደሮች በምስራቅ ኮንጎ እንደሚገኙ እና ኪጋሊ ቡድኑን በእርግጥም እንደምትቆጣጠር አመላክቷል። ኪጋሊ በበኩሏ ከሩዋንዳ የዘር ማጥፋት ጋር ግኑኝነት አለው የምትለው የሩዋንዳ ነፃ አውጪ ዲሞክራሲያዊ ኃይል፤ በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ይደገፋል ስትል ትከሳለች። የተመድ ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ግጭቱ ወደ ቀጣናዊ ጦርነት ከመቀየሩ በፊት ድርድር እንዲጀመር አሳስበዋል። ከኤም23 ጋር አልደራደርም ያሉት ፕሬዝዳንት ሺሴኬዲ፤ በአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ ላይ ሳይካፈሉ ቀርተዋል። በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0