የዩኤስኤአይዲ የገንዘብ ድጋፍ ኢትዮጵያ በውጪ ዕርዳታ ላይ ጥገኛ እንድትሆን እና የራሷን የማህበራዊ ደህንነት አገልግሎት ለመገንባት የምታደርገውን ጥረት ገቷል ሲሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ተናገሩ

ሰብስክራይብ
የዩኤስኤአይዲ የገንዘብ ድጋፍ ኢትዮጵያ በውጪ ዕርዳታ ላይ ጥገኛ እንድትሆን እና የራሷን የማህበራዊ ደህንነት አገልግሎት ለመገንባት የምታደርገውን ጥረት ገቷል ሲሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ተናገሩ "የአፍሪካ ሀገራት ለመሠረታዊ የጤና ወይም የትምህርት አገልግሎቶች በዩኤስኤአይዲ ላይ ጥገኛ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል። የመንግሥት በጀት ዩኤስኤአይዲ ከሚለቀው ጋር ሲነፃፀር በጣም አነስተኛ ነው። የትምህርት ወይም የጤና አገልግሎት ስርዓታችን ወድቋል። አብዛኞቹ ቁልፍ የአገልግሎት ፕሮግራሞች በዩኤስኤአይዲ የሚደገፉ ናቸው። ለዚህም ነው እነዚህን አገልግሎቶች በሀገር ውስጥ ስርዓት ወይም በሀገር በቀል ዕውቀት እንዴት መገንባት እንዳለብን የተሳነን" ሲሉ ኢትዮጵያዊው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች መሱድ ገበየሁ ለስፑትኒክ ተናግረዋል። የትራምፕ አስተዳደር የሚያካሂደው ማሻሻያ፤ ይህንን ታሪክ ከማስቀጠል ይልቅ የአፍሪካ መንግሥታት ለዜጎቻቸው መሠረታዊ አገልግሎቶች የማቅረብ አቅማቸውን የሚያጠናክር፤ የተሻለ የአሜሪካ የዕርዳታ ስርዓት ይፈጥራል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ገልጸዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0