ሩሲያ የእስራኤል እና ሐማስ የተኩስ አቁም ስምምነት አተገባበር እንዳሳሰባት ላቭሮቭ ተናገሩ

ሰብስክራይብ
ሩሲያ የእስራኤል እና ሐማስ የተኩስ አቁም ስምምነት አተገባበር እንዳሳሰባት ላቭሮቭ ተናገሩ ሁለቱ አካላት ስምምነት በመጣስ እንደሚካሰሱ እና የእስራኤል አመራር ከአሜሪካ ተወካዮች ጋር በመሆን ወታደራዊ ዘመቻውን ለመቀጠል በመዛት ላይ እንደሚገኝ፤ ሚኒስትሩ ከሱዳን አቻቸው ጋር ካደረጉት ውይይት በኋላ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል። "በእርግጥም በጣም አሳዛኝ ነው የሚሆነው። ከአረብ ባልደረቦቻችን እና ከሌሎች የተመድ አባል ሀገራት ተወካዮች ጋር በምናደርገው ግንኙነት ይህን ለማስቆም እንሞክራለን" ብለዋል ላቭሮቭ። ላቭሮቭ፤ ለብዙ ዓመታት የቆየው የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ዘላቂ መፍትሄ የሚያገኘው፤ ፍልስጤማውያን ነፃ ሀገር የመፍጠር ሕጋዊ መብት ሲያገኙ ብቻ ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ሃማስ እስከ ቅዳሜ ድረስ ታጋቾችን የማይለቅ ከሆነ፤ እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ወታደራዊ ዘመቻዋን ትቀጥላለች ሲሉ ማክሰኞ እለት ተናግረዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0