40 ያህል የሩሲያ የውጊያ ማሰልጠኛ ያክ-130ኤም ጀቶች ለእስያ ፓስፊክ እና ለአፍሪካ ሀገራት ሊሸጡ እንደሚችሉ የሩሲያ የጦር መሳሪያ ላኪ ድርጅት አስታወቀ

ሰብስክራይብ
40 ያህል የሩሲያ የውጊያ ማሰልጠኛ ያክ-130ኤም ጀቶች ለእስያ ፓስፊክ እና ለአፍሪካ ሀገራት ሊሸጡ እንደሚችሉ የሩሲያ የጦር መሳሪያ ላኪ ድርጅት አስታወቀ ግዙፉ የሩሲያ መንግሥት የመከላከያ ኢንዱስትሪ ድርጅት ሮሶቦሮን ኤክስፖርት ከሩሲያ መከላከያ ኮርፖሬሽን ሮስቴክ እና ዩናይትድ ኤርክራፍት ኮርፖሬሽን ጋር በመሆን የተሻሻለውን የውጊያ ማሰልጠኛ ያክ-130ኤም ጀት፤ በአርሚ-2024 ኤግዚቢሽን ላይ ለበርካታ የውጭ ደንበኞች በማቅረብ ፍላጎቶችን መሳብ እንደቻለ ተገልጿል። "በተጨማሪም በርካታ ሀገራት የያክ-130 ማሰልጠኛዎቻቸውን ማዘመን ይፈልጋሉ። ደንበኛ ሊሆኑ የሚችሉ ሀገራት የሩሲያ ወታደራዊ አቪዬሽን መሳሪያዎችን የሚያንቀሳቅሱትን ይጨምራል" ሲሉ የሮሶቦሮን ኤክስፖርት ዋና ዳይሬክተር አሌክሳንደር ሚኪዬቭ በኤሮ ኢንዲያ 2025 ኤግዚቢሽን መክፈቻ ዋዜማ ላይ ተናግረዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0