የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ዋና ዳይሬክተር የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ አደነቁ

ሰብስክራይብ
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ዋና ዳይሬክተር የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ አደነቁ ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ ይህን የገለጹት፤ ከገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ፣ ከብሔራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ እና ከፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ ጋር በተወያዩበት ወቅት ነው። በውይይቱ ኢትዮጵያ እየተገበረችው በሚገኘው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ላይ ምክክር ተደርጓል። የአይ ኤም ኤፍ ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ የኢትዮጵያ መንግስት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት አድንቀዋል።ምክክሩ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በሆኑት የፊስካል ፖሊሲ ሥራዎች እና የፋይናንስ ዘርፉን ለማዘመን በሚከናወኑ አበይት ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገ ነበር ተብሏል። ፋይናንስ ሚኒስትሩ አሕመድ ሺዴ፤ የኢኮኖሚወን ማሻሻያ በተመለከተ ማብራሪያ እንደሰጡ እና ኢትዮጵያ በአፍሪካ የብልጽግና ምልክት ለመሆን ቆርጣ እየሰራች እንደሆነ መግለጻቸውን ከገንዘብ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያሳያል። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0