ሩሲያ በአዲሰ አበባ ለሚገኘው የሩሲያ ቀይ መስቀል ሆስፒታል መልሶ ግንባታ እገዛ ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን አስታወቀች

ሰብስክራይብ
ሩሲያ በአዲሰ አበባ ለሚገኘው የሩሲያ ቀይ መስቀል ሆስፒታል መልሶ ግንባታ እገዛ ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን አስታወቀችበሩሲያ የጤና ሚኒስትር ሚክሀል ሙራሽኮ እና በሩሲያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ገነት ተሾመ ጂሩ መሀከል የተደረገውን ውይይት ተከትሎ፤ ሩሲያ እና ኢትዮጵያ በጤና ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ ተስማማተዋል። በውይይታቸው ለዶክተሮች ስለሚሰጥ ፕሮፌሽናል ስልጠናም አንስተዋል። ሙራሽኮ እንዳሉት ከ80 በላይ ኢትዮጵያውያን ስፔሻሊስቶች በእናቶች እና ህፃናት ህክምና ዙሪያ በሩሲያ ስልጠና ወስደዋል። እንደ የጤና ሚኒስትሩ ገለጻ ጥልቀት ባላቸው የህክምና ዘርፎች ላይ ለኢትዮጵያውያን ስፔሻሊስቶች ስልጠና ለመስጠት ሩሲያ ዝግጁ ናት።የሩሲያ ባለብዙ የህክምና ዘርፎች ማእከል ሆኖ በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ የተቋቋመው  እና በደጅአዝማች ባልቻ ስም የተሰየመው የሩሲያ ቀይ መስቀል ሆስፒታል፤ የሩሲያ እና የኢትዮጵያ ህዝቦች ወዳጅነት ምልክት ነው። የህክምና ተቋሚ በየአመቱ ከ60,000 በላይ ህመምተኞችን እንደሚቀበል የሩሲያ የጤና ሚንስትር ገልጸዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0