በአቢጃን የሚገኘው የፈረንሳይ የጦር ሰፈር  በጎርጎሮሳዊያኑ የካቲት ወር መጨረሻ ለኮትዲቯር ይተላለፋል ተባለ 

ሰብስክራይብ
በአቢጃን የሚገኘው የፈረንሳይ የጦር ሰፈር  በጎርጎሮሳዊያኑ የካቲት ወር መጨረሻ ለኮትዲቯር ይተላለፋል ተባለ  በመጪው በየካቲት 13 ሊደረግ የታቀደው ርክክብ ሰነስረአት ላይ የሁለቱም ሀገራት የመከላከያ ሚኒስትሮች እንደሚገኙ የፈረንሳይ ሚዲያ ዘግቧል።በጎርጎሮሳዊያኑ ጥር ወር ውስጥ የኮትዲቯር ጦር  በአቢጃን ፖርት - ቦኤት ወደሚገኘው ወደ 43ተኛው የባህር ጦር ባታሊዮን ውስጥ መግባቱ ይታወሳል።የፈረንሳይ ጦር እየወጣ የሚገኘው ፕሬዝዳንት ኦታራ፤ ለአዲስ አመት ባስተላለፉት መልእክት በኮትዲቯር ያለውን የፈረንሳይ ጦር እንዲወጣ መወሰናቸውን ተከትሎ ሲሆን ለዚህም የጦር ሰፈር ርክክብ ዝግጅት ተከናውኗል። ቀስበቀስ ከአፍሪካ አህጉር ውስጥ እየወጣየሚገኘው የፈረንሳይ ጦር እስካሁን ከማሊ፣ ከቡርኪናፋሶ፣ ከኒጀር እና ከቻድ ወጥቷል። በጎርጎሮሳዊያኑ 2025 መጨረሻ ከሴኔጋል እንደሚወጣ ይጠበቃል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0