የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአለምአቀፉ የወንጀለኞች ፍርድቤት በአሜሪካ እና በእስራኤል ላይ  ምንም አይነት እርምጃ እንዳይወስድ ማእቀብ የሚጥል የዋና ትእዛዝ ፊርማቸውን አኖሩ

ሰብስክራይብ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአለምአቀፉ የወንጀለኞች ፍርድቤት በአሜሪካ እና በእስራኤል ላይ  ምንም አይነት እርምጃ እንዳይወስድ ማእቀብ የሚጥል የዋና ትእዛዝ ፊርማቸውን አኖሩ" አሜሪካን ይህንን ማእቀብ በሚተላለፉ የአለምአቀፉ ወንጀለኞች ፍርድቤት (አይሲሲ)  አካላት የሚታይ እና ተጨባጭ የሆነ ወጤት ይኖረዋል ፤ ይህም የንብረት እና ሀብት እገዳ ፤ የአይሲሲ ባለስልጣናት  ፣ ተቀጣሪዎች እና ወኪሎቻቸው እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ የሚጣል የጉዞ ገደብ ሲኖር ወደ ሀገራችን የሚገቡት በእኛ ውሳኔ እና ለአሜሪካ ፍላጎት በተመቸ መልኩ ነው መሆን ያለበት" ሲል መግለጫው ይነበባል ።ይህ የአይሲሲ 'መተላለፍ'  በአሜሪካውያን  እና  በአጋሮቻቸው እስራኤላውያን ጨምሮ ላይ የከፈተ የምርመራ መዝገብ መሆኑን ጨምሮ አስረድቷል። " አይሲሲ በአሜሪካም ሆነ በእስራኤል ላይ ምንም አይነት የዳኝነት ስልጣን የለውም ፤ ሀገራችን የሮም ስብስብ ሆነ የአይሲሲ አባል አይደለችም። ሀገራችንን ለአይሲሲ ዳኝነት እውቅና ሰጥታ አታውቅም እናም ሁለቱም ሀገራት ደሞክራሲን የሚያፀኑ እና የጦርነት ህግን አክብሮ የሚቀሳቀስ ጦር ነው ያላቸው " በማለት ፕሬዝዳንት ትራምፕ በትእዛዛቸው ላይ አስፍረዋል።ከፕሬዝዳንቱ በተጨማሪ  ፤ ከሁለቱ የአሜሪካ ፓርቲዎች የተወጣጡ የሴኔት መሪዎች በአይሲሲ ላይ የሚተገበር ህግን በትጋት እንደሚወጡ ከእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ጋር በነበራቸው ውይይት ወቅት መነሳቱን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ አስታውቋል ።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0