የአሜሪካው ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (ዩኤስ ኤአይዲ) ሚሊዮን ዶላሮችን አወዛጋቢ በሆኑ ፕሮጀክቶች ላይ አባክኗል ሲል ዋይት ሀውስ ገለጸ

ሰብስክራይብ
የአሜሪካው ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (ዩኤስ ኤአይዲ) ሚሊዮን ዶላሮችን አወዛጋቢ በሆኑ ፕሮጀክቶች ላይ አባክኗል ሲል ዋይት ሀውስ ገለጸ ዋይት ሀውስ ባወጣው መግለጫ "የአሜሪካው ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (ዩኤስ ኤአይዲ) ለአስርተ ዓመታት ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ፤ አላስፈላጊ- እና በአብዛኛው ለቢሮክራቶች ክፉ ግላዊ ፕሮጄክቶች ከግብር ከፋዮች ጥያቄ ውጪ እና ያለምንም ቁጥጥር ሲያፈስ ቆይቷል" ብሏል። የሚዲያ ዘገባዎችን የጠቀሰው ዋይት ሀውስ የዩኤስ ኤአይዲን ምዝበራ እና ብልሹ አሰራር የሚያሳዩ ምሳሌዎችን ዘርዝሯል። ከነዚህም ውስጥ በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር ለቬትናም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች፣ ለኤልጂቢቲ* እንቅስቃሴ፣ ለግብፅ የቱሪዝም ዘርፍ ድጋፍ፣ በቻይና ዉሃን ቤተ ሙከራ በምርምር ውስጥ ለተሳተፈው ኢኮሄልዝ አሊያንስ እንቅስቃሴ እና ከአሸባሪ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት ላላቸው ፕሮጀክቶች ሲፈስ መቆየቱ ተገልጿል። * "የኤልጂቢቲ እንቅስቃሴ" በሩሲያ መንግሥት በፅንፈኝነት የተፈረጀ እና በሩሲያ ውስጥ የተከለከለ ነው።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0