የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ እና በሩሲያ ፌድሬሽን ምክርቤት  የአለም አቀፍ ጉዳዩች ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አንድሬይ ክሊሞቭ  ተወያዩ

ሰብስክራይብ
የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ እና በሩሲያ ፌድሬሽን ምክርቤት  የአለም አቀፍ ጉዳዩች ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አንድሬይ ክሊሞቭ  ተወያዩ በውይይታቸው ወቅት፤ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር ማእረግ የዲሞክራሲ ማስተባበሪያ ማእከል ሀላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማት፣ በግብርና፣ በኢንፎርሜሽን እና ኮሚኒኬሽን፣ በኢንዱስትሪ እና ሌሎችም ዘርፎች ስኬታማ ጉዞ እና ፈጣን እድገት እያስመዘገበች ነው ብለዋል። የብሪክስ አባል ሀገር መሆኗ ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲ ዘርፍ ከብዙ ሀገራት ጋር  ያላትን ግንኙነት እንድታጠነክር እድል ሰጥቷታል ሲሉም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል። የሩሲያው ባለስልጣን በበኩላቸው ሁለቱ ሀገራቱ የቆየ እና ጠንካራ ታሪካዊ ግንኙነት እንዳላቸው አስታውሰዉ ፤ በብልፅግና ፓርቲ ጉባኤ ላይ በመጋበዛቸዉ የላቀ ምስጋናቸውን እና አክብሮታቸውን አቅርዋል። ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በግብርና እና በሌሎችም ዘርፍ ያላቸውን ትብብር አጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን ክሊሞቭ አረጋግጠዋል ሲሉ ሚዲያዎች ዘግበዋል። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0