የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ከሆኑት ኢቭጌይኒ ተርኪኺን ጋር ውይይት አደረጉ

ሰብስክራይብ
የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ከሆኑት ኢቭጌይኒ ተርኪኺን ጋር ውይይት አደረጉ ዶክተር መቅደስ ከሩሲያው አምባሳደር ኢቭጌይኒ ተርኪኺን ጋር በጤና ዘርፍ አብሮ ስለመስራት ተወያይተዋል።የጤናው ዘርፍ ሁለቱ ሀገራት ለበርካታ ዘመናት በቆየ ወዳጅነታቸው ከሚሰሩባቸው ዘርፎች አንዱ እንደሆነና ሀገራቱ  ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሰሩ የጤና ሚኒስትሯ ተናግረዋል። በተለይም የህክምና ግብአቶችን እና መድሀኒቶችን በመደገፍ፣ የሀገር ውስጥ የመድሀኒት አምራቾችን በማበረታታት፣ ለድንገተኛ ህብረተሰብ የጤና አደጋዎች ፈጣን ምላሽ በመስጠት እና ክትባቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት ስለሚቻልባቸው ጉዳዩች ከልኡካኑ ጋር ተወያይተዋል።በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌይን ተርኪኺን በበኩላቸው በድንገተኛ አደጋዎች ዙሪያ የሚሰጠውን ምላሽ ለማጠናከር ስልጠና እና የልምድ ልውውጦች እንደሚደረጉ ገልፀዋል። ምስል የጤና ሚኒስትር የማህበራዊ ትስስር ገፅ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0