ፈርተዋልን? የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዳ ትራምፕ ካናዳን በተመለከተ ለሰጡት አስተያየት ምላሽ ሰጥተዋል

ሰብስክራይብ
ፈርተዋልን? የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዳ ትራምፕ ካናዳን በተመለከተ ለሰጡት አስተያየት ምላሽ ሰጥተዋልፕሬዝዳንት ትራምፕ "ተገቢ ያልሆነ የቀረጥ ክፍያን" በሀገራቸው ላይ ተግባራዊ የሚያደርጉ ከሆነ ካናዳ "ከባድ የሆነ ምላሽ" እንደምትሰጥ እና አሜሪካ የጥሬ እቃ አቅርቦቷን ከሩሲያም ቢሆን ማግኘት ሊኖርባት እንደሚችል ተናግረዋል። የካናዳው መሪ ትራምፕ ለአሜሪካ ቃል የገቡት "ወርቃማ ዘመን" ተጨማሪ ማእድናት፣ ብረት፣ እና አልሙንየም እንዲሁም ተመጣጣኝ እና ሁነኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ያስፈልገዋል ብለዋል።"ካናዳ እነዚህ ሁሉ ሀብቶች አሏት፤ በተጨማሪም ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በጋራ በመሆን የሰሜን አሜሪካን ኢኮኖሚ በይበልጥ ለማሳደግ ዝግጁ ነን" ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል። "ሌላው አማራጭ ከሩሲያ፣ ቻይና እና ቬንዙዌላ ጥሬ እቃዎችን ማግኘት ነው። ካናዳ ደህንነቷ የተጠበቀ፣ ከስጋት ነፃ የሆነች እና እርግጠኛ ባልሆነ ዓለም ተዓማኒ አጋር ናት"  ሲሉም አክለዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0