የጥር 9 ረፋድ አበይት የዓለም ጉዳዮች፦

ሰብስክራይብ
የጥር 9 ረፋድ አበይት የዓለም ጉዳዮች፦ 🟠 የኢራን ፕሬዝዳንት ማሱድ ፔዝሽኪያን ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ሞስኮ ገቡ። 🟠 እስራኤል፣ ሃማስ፣ አሜሪካ እና ኳታር ታጋቾችን በመልቀቅ እና በጋዛ ሰርጥ የተኩስ አቁም ትግበራ ዙርያ በይፋ ስምምነት መፈራረማቸውን የአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። 🟠 የአሜሪካ ፕሬዝዳንቶች ስልጣናቸው ሲገባደድ ከነበራቸው የህዝብ ተቀባይነት አንጻር፤ ጆ ባይደን ከ1938 በኋላ በከፍተኛው የሕዝብ ተቀባይነት ካጡ ፕሬዝዳንቶች አንዱ ሆነው ስልጣናቸውን እንደሚለቁ ተገለጸ። 🟠 በግሪንላንድ የሚገኙ የዩናይትድ ስቴትስ ጦር ሰፈሮች ደሴቲቱ ነጻነቷን ብታገኝም ባሉበት እንደሚቆዩና ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች በዚህ እንደሚስማሙ የፓርላማ አባል እና የግሪንላንድ የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፔሌ ብሮበርግ ተናገሩ። 🟠 ሰባተኛው የስታርሺፕ ሙከራ እንዳልተሳካና የጠፈር መንኮራኩሯ እንደወደመች የተገለጸ ሲሆን የስፔስ ኤክስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢሎን መስክ አደጋው በነዳጅ መፍሰስ ምክንያት እንደተከሰተ ጠቁሟል። 🟠 ሩሲያ በቱርክስትሪም የነዳጅ ማስተላለፊያ ላይ የተፈጸመው የዩክሬን ጥቃት በዋሽንግተን እና በለንደን ጥቆማ የተፈፀመ መሆኑን ለማመን በቂ ምክንያት አላት ሲሉ በመንግስታቱ ድርጅት የሩሲያ ቋሚ ተወካይ ቫሲሊ ንቤንዝያ ተናግረዋል። 🟠 አሜሪካዊው የፊልም ዳይሬክተር እና የኦስካር አሸናፊ ዴቪድ ሊንች ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለየ ቤተሰቡቹ በማህበራዊ ትስስር ገጽ ባሰፈሩት ጽሁፍ ገልጸዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0