በቻድ ፕሬዝዳንታዊ ቤተ-መንግሥት ላይ የተፈጸመው ጥቃት የግድያ ሙከራ ነው ሲሉ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ተናገሩ

ሰብስክራይብ
በቻድ ፕሬዝዳንታዊ ቤተ-መንግሥት ላይ የተፈጸመው ጥቃት የግድያ ሙከራ ነው ሲሉ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ተናገሩ በፕሬዝዳንታዊ ቤተ-መንግሥቱ ላይ የተነጣጠረውን ጥቃት አስመልክቶ ጥር 10 ቀን ንግግር ያደረጉት ፕሬዝዳንት ማሃማት ኢድሪስ ዴቢ ኢትኖ "የዚህ ከንቱ ሙከራ ፈጻሚዎች ሃሳባቸው የእኔን ህይወት ማጥፋት ነበር። ሆኖም በፕሬዝዳንታዊ ዘቦች ጀግንነት፣ ንቃት እና ወኔ ተወግደዋል" ብለዋል። ፕሬዝዳንት ኢትኖ ድርጊቱን “የማተራመስ ሙከራ” ሲሉም ገልፀውታል። ታህሳስ 30 አመሻሽ “24 ክፉ ዓላማ ያነገቡ ግለሰቦች ተሽከርካሪያቸው ብልሽት እንደገጠመው አስመስለዋል” ሲል አቃቤ ህግ አስታውቋል። ከዚያም በቤተ-መንግሥቱ መግቢያ በር ላይ የነበሩትን በርካታ ጠባቂዎች በቢላዋ አጥቅተዋል። በምላሹም 18 አጥቂዎች ሲገደሉ ስድስቱ ደግሞ ቆስለዋል። አንድ የፕሬዝዳንታዊ ዘብ ሲገደል፤ ሌሎች ሶስት ዘቦች ከነዚህም ውስጥ ሁለቱ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0