የፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮንን ንግግር አስመልክቶ ፈረንሳይ ፤ በሀገር ውስጥ ጉዳዩቼ ጣልቃ እየገባች ነው በማለት አልጄሪያ ከሰሰች

ሰብስክራይብ
የፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮንን ንግግር አስመልክቶ ፈረንሳይ ፤ በሀገር ውስጥ ጉዳዩቼ ጣልቃ እየገባች ነው በማለት አልጄሪያ ከሰሰች ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የፀሀፊውን የቦኣለም ሳንሳል እስርን አስመልክቶ ያሰሙት ንግግር በሀገር ውስጥ ጉዳያችን ጣልቃ መግባት ነው በማለት የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ አስታወቀ።አፍሪካዊቷ ሀገር የፀሀፊውን ነፃነት ነጥቃዋለች ፤ በማለት ከዚህ ቀን ቀደም ብሎ፤ ማክሮን ስለ ፈረንሳይ - አልጄሪያን ዜግነት ያለውን ቦኣለም ሳንሳል  ከእስር መፈታት ጠይቀዉ ነበር። " የአልጄሪያ መንግስት የፈረንሳዩን ፕሬዝዳንት ሰለ አልጄሪያ ያሰሙትን ንግግር በአግርሞት አስተውሎታል።  እነዚህ ቃላት  ተገቢነት የሌላቸው፣ ተቀባይነት  የሌላቸው እና መነቀፍ ያለባቸው ብቻ ናቸው፤ በአልጄሪያ የውስጥ ጉዳዮች ላይ የሚደረግ ጣልቃ ገብነት እና በድፍረት የሚደረግ ንግግር ተቀባይነት የሌለዉ ነው" በማለት የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በመግለጫው  አስታውቋል። ከዚህ ቀደም በ ጎርጎሮሳውያኑ 2015 በፃፈዉ መፅሀፍ ምክንያት  የፈረንሳይ አካዳሚ ሽልማትን የወሰደው እና ከቀናቶች በፊት ባለቀዉ የጎርጎሮሳውያኑ አመት የፈረንሳይ ዜግነት ያገኘው የ75 አመቱ ቦኣሌም በአልጄሪያ በእስር ላይ ይገኛል። ለእስር የተዳረገበት ምክንያት አልታወቀም።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦  APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0