ከቻድ ጋር የነበራት የጦር ትብብር ስምምነት ማለቁን አስመልክቶ ፈረንሳይ ወታደሮቿን ማስወጣት ቀጥላለች

ሰብስክራይብ
  ከቻድ ጋር የነበራት የጦር ትብብር ስምምነት ማለቁን አስመልክቶ ፈረንሳይ ወታደሮቿን ማስወጣት ቀጥላለችበትላንትናው እለት ከ ቀኑ 11:30 አካባቢ 70 የፈረንሳይ ወታደሮች ከኒጃሜና አየር ማረፊያ መነሳታቸውን የቻድ ተጣቂ ኃይሎች ሚኒስትር ተናግረዋል። የተሳፈሩበት ኤ330 ኤርባስ አውሮፕላን ስምንት ቶን ካርጎ ተጭኖበት ነበር። ከሳምንት በፊት ሌላ የፈረንሳይ ወታደሮች ቡድን ሀገሪቱን ለቀው ወጥተዋል። ኒጃሜና ከፓሪስ ጋር የነበራትን የጦር ትብብር ስምምነት በህዳር ወር መጨረሻ  ማቋረጧን አስታውቃ ነበር። የውጊያ ጀቶቹ ከሄዱ በኋላ የመጀመሪያው 120 ወታደሮችን የያዘ ቡድን በጎርጎሮሳዊያኑ ታህሳስ 20 ነበር ሀገሪቱን የለቀቀዉ። በጎርጎሮሳዊያኑ ታህሳስ 26, የፋያ ላርጊዩ የጦር ሰፈር በይፋ ከፈረንሳይ ኃይሎች ወደ ቻድ ጦር ተላልፏል። ቻድ አሁን ላይ ከጎርጎሮሳዉያኑ ጥር 31 በፊት የፈረንሳይ ጦር ሀገሪቷን ሙሉ ለሙሉ ለቀዉ እንዲወጡ ትፈልጋለች።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦  APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0