ሱዳን ከፈጥኖ ደራሽ ኃይል ጋር ያለውን ግጭት ለመፍታት የቱርክን አሸማጋይነት ተቀበለች

ሰብስክራይብ
ሱዳን ከፈጥኖ ደራሽ ኃይል ጋር ያለውን ግጭት ለመፍታት የቱርክን አሸማጋይነት ተቀበለችየሱዳን ጦር አዛዥ አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን በሀገሪቱ ለ20 ወራት የዘለቀውን ግጭት ለመፍታት ቱርክ ያቀረበችውን የድርድር ጥያቄ እንደሚደግፉ ገልጸዋል። ቡርሃን በፖርት ሱዳን በተደረገው ስብሰባ ለቱርኩ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶዋን የሰላም ተነሳሽነት ድጋፋቸውን ለቱርክ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቡርሃንቲን ዱራን ገልፀዋል። የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሊ ዩሱፍ፤ ሱዳን እንደ ቱርክ ያሉ አጋሮች ጥምረት እንደሚያስፈልጋት ገልጸው ፣ ይህ ተነሳሽነት ለሰላም መንገድ ሊከፍት እንደሚችል ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል። ኤርዶጋዋን በዚህ ወር በስልክ ባደረጉት ንግግር በሱዳን እና በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ መካከል ያለውን ውጥረት ጨምሮ ግጭትን ለመፍታት የቱርክ ሚና እንትጫወት ሀሳብ አቅርበው ነበር። የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ውድቅ ብታደርገውም የሱዳን ፈጠኖ ደራሽ ኃይልን ትደግፋለች የሚል ክስ ይቀርብባታል። ዱራን ቱርክ ሰላምን ለማጠናከር የክልል ተዋናዮችን ለማሳተፍ ዝግጁ መሆኗን ሲገልጹ፤ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ደግሞ ከቱርክ የዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች ጋር ለመተባበር ፈቃደኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦  APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0