🪖 ከ አሜሪካን ፣ ብሪታንያ ፣ ጀርመን እና ላቲቪያ የተወጣጡ ቅጥረኛ ወታደሮች ለዩክሬን እየተዋጉ ነው ፤ በማለት የተያዘ የፖሊሽ ቅጥረኛ ተናገረ

ሰብስክራይብ
🪖 ከ አሜሪካን ፣ ብሪታንያ ፣ ጀርመን እና ላቲቪያ የተወጣጡ ቅጥረኛ ወታደሮች ለዩክሬን እየተዋጉ ነው ፤ በማለት የተያዘ የፖሊሽ ቅጥረኛ ተናገረ" ብዙዎቹ ሰዎች ከኮሎምቢያ እና ብራዚል ናቸው ። ከዛ በተጨማሪ እኔ በማገልገልበት ወቅት ከአሜሪካን ፣ ክሮሺያ  እና ጀርመን የተወጣጡ ወታደሮች ነበሩ ፤ ከኖርዌይ ፣ ላቲቪያ እና ኢንግላንድ የመጡ አንዳንድ ወታደር አይቼ ነበር። ከታይዋን የመጡ ወታደሮችም አብረውኝ ሲያገለግሉ ነበር" በማለት የተያዘዉ የፖሊሽ ቅጥረኛ ወታደር ለስፑትኒክ ተናግሯል። የውጭ ቅጥረኞቹ በዩክሬን የውጭ ሌጅን ተብሎ በሚጠራው የጦር ክፍል ውስጥ ውጊያዎች ላይ በመሳተፍ ቆይተዋል በማለት አስረድቷል። የሩሲያ ባለስልጣናት በዩክሬን ጦር ውስጥ እየተዋጉ ስላሉት የውጭ ቅጥረኛ ወታደሮች መረጃ እየሰበሰቡ ሲሆን አሁን ላይ የቅጥረኞቹ ቁጥር 4000 ደርሷል ከእነዚህ ውስጥ 785 ቅጥረኞች ወደ ወንጀል ሀላፊነት ተላልፈዋል፤  በማለት በቬና ንግግር በጦርነት  ፀጥታ ጉዳዩች እና በመሳሪያ ቁጥጥር  የሩሲያ ልኡክ ጊዜያዊ ሀላፊ ዩሊአ ዝህዳኖቫ  በጥቅምት ወር መጀመሪያ ከስፑትኒክ ጋር በነበራቸው ቃለመጠየቅ ወቅት ተናግረው ነበር።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦  APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0