የሳይበር ትራክ ፍንዳታ 'በርችት ወይም ቦምብ' የተፈጸመ 'የሽብር ድርጊት' ነው ሲል ኤለን መስክ ተናገረ

ሰብስክራይብ
የሳይበር ትራክ ፍንዳታ 'በርችት ወይም ቦምብ' የተፈጸመ 'የሽብር ድርጊት' ነው ሲል ኤለን መስክ ተናገረ የቴስላ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኤለን መስክ ክስተቱ "ከተሽከርካሪው ጋር የተገናኛ እንዳልሆነ" አፅንዖት ሰጥቷል። በፍንዳታው ወቅት ሁሉም የመኪናው ሲስተሞች በአግባቡ እየሰሩ እንደነበር መስክ ጨምሮ ገልጿል። መስክ በኒው ኦርሊንስ የተፈጸመው የሽብር ጥቃት እና በላስ ቬጋስ የተከሰተው የሳይበር ትራክ ፍንዳታ 'በተወሰነ መንገድ ሊገናኙ' እንደሚችሉ ተናግሯል። በላስ ቬጋስ ትራምፕ ኢንተርናሽናል ሆቴል አካባቢ በደረሰው ፍንዳታ የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ ሰባት ሰዎች ቆስለዋል። የላስ ቬጋስ ፖሊስ መምሪያ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን አረጋግጧል። የሕግ አስከባሪ አካላት ድርጊቱ የሽብር ጥቃት ሊሆን እንደሚችል መግለጻቸውን ኤቢሲ ኒውስ ዘግቧል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0