ዙምባቡዌ ያለባትን የኃይል አጥረት ለመቅረፍ ከሩሲያ እና አይኤኢ ጋር በኑክሌር ኃይል ላይ ትብብር ልትፈጥር ነው

ሰብስክራይብ
ዙምባቡዌ ያለባትን የኃይል አጥረት ለመቅረፍ ከሩሲያ እና አይኤኢ ጋር በኑክሌር ኃይል ላይ ትብብር ልትፈጥር ነው የኃይል ሚኒስትሩ ኤድጋር ሞዮ የዙምባቡዌ ከእነዚህ አጋሮች ጋር በመሆን አነስተኛ ሞዱላር ሪአክተርስ (ለኃይል ፍላጎቶች የሚሆኑ የኑክሌር ማስተላለፊያዎች ) የማልማት ፍላጎት እንዳላት አሳውቀዋል። " የምንፈልግበት ቦታ እንድንደርስ እርምጃዎቻችንን ለመደገፍ ፍቃደኝነታቸውን አሳይተውናል" ብለዋል ተብሎ ሚኒስትሩ ተጠቅሰዋል። በጎርጎሮሳዊያኑ 2035 ሀገሪቱ የምታመርተውን የኃይል መጠን ወደ 4000 ሜጋዋት ለማሳደግ እቅድ የያዘች ሲሆን ይህም በኃይል ዘርፍ ራሷን ለመቻል የምታደርገው ጥረት ወሳኝ ለውጥ ይሆናል በማለት ሪፖርቱ ዘግቧል።  ከኑክሌር ኃይል ጎን ለጎን ሀገሪቱ ከታዳሽ ሀይሎች የምታገኘውን ኃይል በ2030 ወደ 2000 ሜጋዋት ለማሳደግ እቅድ የያዘች ሲሆን ፀሀይ ፣ ንፋስ እና አነሰተኛ የኤሌትሪክ ግድቦች የታዳሽ ኃይሉ አመንጪዎች ናቸው።አሁን ላይ ሀገሪቱ የምታመነጨው 2600 ሜጋዋት የሚደርስ ኃይል እነዚህ ትብብሮች ሲጨምሩበት የኃይል መቆራረጡን የሚያስቀር ፣ የሀገሪቱን የኃይል አቅም የሚያስድግ እና ካለችበት ሁኔታ የሚያስወጣ ነው።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦  APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0