የአፍሪካ ህብረት በሞዛምቢክ የተከሰተው የርስ በርስ አለመረጋጋት ሰላማዊ መፍትሄ እንዲፈታ ጥሪ አቀረበ"የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሃማት መንግስት እና ሁሉም የፖለቲካ እና ማህበራዊ ተዋናዮች ተጨማሪ የህይወት መጥፋትን እና የንብረት ውድመትን ለማስወገድ ቀውሱን በሰላማዊ መፍትሄ እንዲፈቱ አሳስበዋል" ሲል ድርጅቱ ሐሙስ ባወጣው መግለጫ ገልጿል።ማሃማት አክለውም የፀጥታ ኃይሎች የኃይል አጠቃቀማቸ በመቆጠብ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል። በተጨማሪም በተከሰተው ሁከቱ ምክንያት የሚወዷቸውን ሰዎች ላጡ ሰዎች ጥልቅ ሀዘናቸውን ገልጸዋል።ሊቀመንበሩ ህብረቱ የዓመፅ ድርጊቱን ለማስቆም እና የሀገሪቱን ዴሞክራሲ ለመጠበቅ ከሞዛምቢክ ባለሥልጣናት ጋር ለመተባበር ዝግጁ መሆኑን በድጋሚ አረጋግጠዋል። ሰኞ ዕለት የሞዛምቢክ ህገ መንግስታዊ ምክር ቤት በጥቅምት ወር የተካሄደውን የምርጫ ውጤት አረጋግጧል። ይህን ተከትሎም በመላ አገሪቱ አመጽ ተነስቷል።በሞዛምቢክ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የመጨረሻ ውጤት መገለጹን ተከትሎ በሞዛምቢክ ዋና ከተማ በተነሳው ተቃውሞ ቢያንስ 50 ሰዎች በጥይት መቁሰላቸውን የሞዛምቢክ መገናኛ ብዙሃን ረቡዕ ዕለት ዘግበዋል። ብሉምበርግ የዜና ወኪል እንደዘገበው በጎርጎርሳውያኑ ጥቅምት 9 ከተካሄደው ምርጫ በኋላ በተቀሰቀሰው ተቃውሞ በአጠቃላይ186 ሰዎች ሞተዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
የአፍሪካ ህብረት በሞዛምቢክ የተከሰተው የርስ በርስ አለመረጋጋት ሰላማዊ መፍትሄ እንዲፈታ ጥሪ አቀረበ
የአፍሪካ ህብረት በሞዛምቢክ የተከሰተው የርስ በርስ አለመረጋጋት ሰላማዊ መፍትሄ እንዲፈታ ጥሪ አቀረበ
Sputnik አፍሪካ
የአፍሪካ ህብረት በሞዛምቢክ የተከሰተው የርስ በርስ አለመረጋጋት ሰላማዊ መፍትሄ እንዲፈታ ጥሪ አቀረበ"የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሃማት መንግስት እና ሁሉም የፖለቲካ እና ማህበራዊ ተዋናዮች ተጨማሪ የህይወት መጥፋትን እና የንብረት... 27.12.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-12-27T15:27+0300
2024-12-27T15:27+0300
2024-12-27T15:44+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
የአፍሪካ ህብረት በሞዛምቢክ የተከሰተው የርስ በርስ አለመረጋጋት ሰላማዊ መፍትሄ እንዲፈታ ጥሪ አቀረበ
15:27 27.12.2024 (የተሻሻለ: 15:44 27.12.2024)
ሰብስክራይብ