የኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጦር በሀገሪቱ ምስራቃዊ ክፍል ስድስት የሩዋንዳ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መቶ ጣለ ሰው አልባ አውሮፕላኖቹ በምስራቃዊ ኮንጎ ሰሜን ኪቩ ግዛት እንደተመቱ፤ የኮንጎ የዜና ወኪል ኤሲፒ ዘግቧል። የአንጎላ መንግሥት መግለጫን ያጣቀሱ የምዕራቡ ዓለም መገናኛ ብዙሃን የኮንጎ እና ሩዋንዳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ከፈረንጆቹ ሰኔ 4 ጀምሮ በኮንጎ አማፂ ቡድኖች በሚታመሱ ክልሎች የተኩስ አቁም ስምምነት ለማድረግ መስማማታቸውን በሐምሌ ወር መጨረሻ ዘግበዋል። ስምምነቱ ሉዋንዳ በሚገኘው ፕሬዝዳንታዊ ቤተ-መንግሥት በአንጎላ ፕሬዝዳንት ጃዎ ሎሬንሶ አመቻችነት ከተደረገ ውይይት በኋላ የመጣ ነው። የተኩስ አቁሙን ለመከታተል የተሻሻለ ልዩ የማረጋገጫ ዘዴ ይዘረጋል ተብሎ ይጠበቅ ነበር። በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና ሩዋንዳ መካከል የተፈጠረውን ግጭት ለማስቆም የተካሄደው ድርድር እንደቆመና ችግሩን ለመፍታት የተዘጋጀው የመሪዎች ጉባኤ መሰረዙን መገናኛ ብዙሃን በቅርቡ ዘግበዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
የኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጦር በሀገሪቱ ምስራቃዊ ክፍል ስድስት የሩዋንዳ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መቶ ጣለ
የኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጦር በሀገሪቱ ምስራቃዊ ክፍል ስድስት የሩዋንዳ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መቶ ጣለ
Sputnik አፍሪካ
የኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጦር በሀገሪቱ ምስራቃዊ ክፍል ስድስት የሩዋንዳ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መቶ ጣለ ሰው አልባ አውሮፕላኖቹ በምስራቃዊ ኮንጎ ሰሜን ኪቩ ግዛት እንደተመቱ፤ የኮንጎ የዜና ወኪል ኤሲፒ ዘግቧል። የአንጎላ መንግሥት መግለጫን... 26.12.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-12-26T14:48+0300
2024-12-26T14:48+0300
2024-12-26T15:14+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
የኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጦር በሀገሪቱ ምስራቃዊ ክፍል ስድስት የሩዋንዳ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መቶ ጣለ
14:48 26.12.2024 (የተሻሻለ: 15:14 26.12.2024)
ሰብስክራይብ