ደቡብ አፍሪካ በሞዛምቢክ የተከሰተው ሁከት እንዳሳሰባት እና ሁሉም ወገኖች ፖለቲካዊ ውይይት እንዲያደርጉ ጥሪ አቀረበች

ሰብስክራይብ
ደቡብ አፍሪካ በሞዛምቢክ የተከሰተው ሁከት እንዳሳሰባት እና ሁሉም ወገኖች ፖለቲካዊ ውይይት እንዲያደርጉ ጥሪ አቀረበች "በሞዛምቢክ ሕገ-መንግሥታዊ ምክር ቤት የታወጀውን የመጨረሻ የምርጫ ውጤት ተከትሎ እየቀጠለ ያለው የተቃውሞ ሁከትና ረብሻ ደቡብ አፍሪካን አሳስቧታል። ደቡብ አፍሪካ ሁሉም ወገኖች ሀገሪቱን ወደ አዲስ የፖለቲካና የልማት አቅጣጫ የሚመራ አስቸኳይ ውይይት እንዲያደርጉ ትጠይቃለች” ሲል የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለጫ ገልጿል። ደቡብ አፍሪካ ሞዛምቢክ ይህንን ውይይት እንድታደረግ ለማመቻቸት በማንኛውም መልኩ ለመርዳት ዝግጁ መሆኗን የገለፀው መግለጫው፤ የሀገሪቱ መንግሥት "አሁን ላለው ችግር ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት ከሳድክ እና ከሌሎች የባለብዙ ወገን ድርጅቶች ጋር ተባብሮ ይሰራል" ብሏል። ሚኒስቴሩ ሁሉም አካላት እንዲቆጠቡ እና እንዲረጋጉም ጠይቋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0