ሱዳን የሩሲያ የባህር ኃይል ሎጂስቲክስ ማዕከልን ለማስተናገድ ፈቃደኛ አለመሆኗን የሚገልጹ ዘገባዎች ሀሰተኛ ናቸው ሲል የሩሲያ ኢምባሲ ገለጸ

ሰብስክራይብ
ሱዳን የሩሲያ የባህር ኃይል ሎጂስቲክስ ማዕከልን ለማስተናገድ ፈቃደኛ አለመሆኗን የሚገልጹ ዘገባዎች ሀሰተኛ ናቸው ሲል የሩሲያ ኢምባሲ ገለጸ የሱዳን የመረጃ ምንጮችን የጠቀሱ በርካታ የምዕራባውያን ሚዲያዎች፤ ካርቱም ከዩናይትድ ስቴትስ ሊጣልበት የሚችለውን ማዕቀብ በመስጋት፤ የሩሲያ የባህር ኃይል የሎጂስቲክስ ማዕከልን ለማስተናገድ ከሞስኮ ጋር የተደረገውን ስምምነት ውድቅ አድርጋለች ሲሉ ዘግበዋል። የሩሲያ ባህር ኃይል የሎጂስቲክስ ማዕከሉን ለማቋቋም በሀገራቱ መካከል የተደረገው ስምምነት በታህሳስ 2020 መጀመሪያ ላይ ነበር ይፋ የሆነው። የሎጂስቲክስ ማዕከሉ ለጥገና፣ ለአቅርቦቶች እና ለሩሲያውያን መርከብ ሠራተኞች ማረፊያነት ጥቅም ላይ እንዲውል የታሰበ ነበር። በሰነዱ መሠረት በሎጂስቲክስ ማዕከሉ ከፍተኛው የሰራተኞች ብዛት ከ300 ሰዎች አይበልጥም። በተመሳሳይ ጊዜ ከአራት በላይ የሩሲያ መርከቦች በማዕከሉ መገኘት አይችሉም።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0