የታህሳስ 14 ምሽት አበይት የዓለም ዜናዎች፦

ሰብስክራይብ
የታህሳስ 14 ምሽት አበይት የዓለም ዜናዎች፦ 🟠 በአፍሪካ ያለው የኤምፖክስ ወረርሽኝ አሳሳቢ እንደሆና በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ፣ ኡጋንዳ እና ብሩንዲ ወረርሽኙ አሁንም ቀጥሏል ሲል የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ። 🟠 የቻይና ፍርድ ቤት ተሽከርካሪውን በአካባቢው ከሚገኝ ትምህርት ቤት መግቢያ በቆሙ ሰዎች ላይ የነዳውን ግለሰብ በሞት ፍርድ ቀጣ። 🟠 የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና የስሎቫኪያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሮበርት ፊኮ ትናንት ያካሄዱት ውይይት፤ ዝርዝርና ለሁለት ሰዓታት የቆየ እንደነበር እንዲሁም አጥጋቢ ውጤት እንደተገኘበት የሩሲያ ፕሬዝዳንት ረዳት ዩሪ ኡሻኮቭ ተናገሩ። 🟠 የጀርመን መንግሥት ሁለት አይሪስ-ቲ የአየር መቃወሚያዎችን እና ሁለት የፓትሪዮት አስወንጫፊዎችን ለዩክሬን እንዳቀረበ፤ ጀርመን ለዩክሬን የሰጠችውን ወታደራዊ ድጋፍ የሚገልጽ ዝርዝር አሳየ። 🟠 ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በሩሲያ ኩርስክ ክልል ከ300 በላይ የዩክሬን ወታደሮች መገደላቸውን እና አንድ አብራምስን ጨምሮ፤ ሁለት ታንኮች መውደማቸውን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0