የሳህል ሀገራት ጥምረት ኃይሉን በተጠንቀቅ እንዲቆም ጠየቀ

ሰብስክራይብ
የሳህል ሀገራት ጥምረት ኃይሉን በተጠንቀቅ እንዲቆም ጠየቀ ቡርኪናፋሶ፣ ማሊ እና ኒጀር፤ ፈረንሳይ እና የኢኮዋስ "ጥቂት መሪዎች" የሳህል መንግሥታት ጥምረትን "ለማተራመስ" ይፈልጋሉ ሲሉ በጋራ ባወጡት መግለጫ ከሰዋል። ሀገራቱ በቻድ ሀይቅ ተፋሰስ፣ በሳህል እና በተወሰኑ የድንበር አካባቢዎች የአሸባሪ ቡድኖችን መልሶ የማደራጀት ዘመቻዎችን ጠቅሰዋል። እንደ የሳህል ሀገራት ጥምረት መግለጫ ከሆነ፤ እነዚህ የሽብር ቡድኖች ከውጭ መንግሥታት የገንዘብ እና የሎጂስቲክስ ድጋፍ ያገኛሉ። በዚህ አውድ ክልሉ “የወታደራዊ ዘመቻ ቲያትር” ተብሎ የታወጀ ሲሆን፤ የመከላከያ እና የጸጥታ ኃይሎች በተጠንቀቅ ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል። የሳህል ሀገራት ጥምረት መሪዎች ህዝቡ "ንቃቱን እንዲጨምር" እና "የአሸባሪ ቡድኖችን የምልመላ ጥሪዎች ውድቅ እንዲያደርጉ" ጥሪ አሳስበዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0