ሩዋንዳ የመጨረሻው በማርቡርግ በሽታ የተየዘ ሰው ውጤት ኔጌቲቭ መሆኑን አስመልክታ የመጀመሪያው የማርቡርግ ወረርሺኝ ማጥፋቱን አውጃለች በማለት የአለም ጤና ድርጅት አሳወቀ

ሰብስክራይብ
ሩዋንዳ የመጨረሻው በማርቡርግ በሽታ የተየዘ ሰው ውጤት ኔጌቲቭ መሆኑን አስመልክታ የመጀመሪያው የማርቡርግ ወረርሺኝ ማጥፋቱን አውጃለች በማለት የአለም ጤና ድርጅት አሳወቀበትላንትናው እለት የሩዋንዳ መንግስት እንዳሳወቀዉ የመጨረሻው በቫይረሱ የተያዘዉ የመጨረሻ ታማሚ በሁለት ግዜ ምርመራ ውጤቱ ነጋቴቭ በመሆኑ እንዲሁም ላለፉት 42 ቀናት አዲስ በበሽታው የተያዘ ሰው አለመኖሩን የአለም ጤና ድርጅት አስታውቋል። " በሩዋንዳ መንግስት የተሰጠው ጠንካራ የሆነ ምላሽ  ትጉህ የሆነ አመራር እና ከአጋሮቹ ጋር ጠንካራ የሆነ የጤና ስረአት የሚያጋጥሙ የህብረተሰብ ጤና ድንገተኛ ችግሮችን ለመፍታት ህይወት ለማዳን እና የግለሰቦችን እና የህብረተሰቡን ጤና ለማስጠበቅ ወሳኝ ነው" በማለት የአለምጤና ድርጅት ተወካይ በሩዋንዳ ብሪያን ቺሮምቦ በመግለጫቸው አስረድተዋል። የሩዋንዳ ባለሥልጣናት፣ የዓለም ጤና ድርጅት እና አጋሮች የተሳተፉበት ፈጣን እና አጠቃላይ ምላሽ፣ ጠንካራ ክትትል፣ ምርመራ፣ የግንኙነት መከታተያ እና የህዝብ ግንዛቤ ዘመቻዎች የተሳካ ሁኔታ የበሽታውን ስርጭት ለመግታት አስችሏል ሲል መግለጫው አመልክቷል።በጎርጎሮሳውያኑ መስከረም 27 ቀን የተረጋገጠው የኢቦላ መሰል በሽታ ወረርሽኝ 66 ሰዎች በበሽታው መያዛቸውንና 15 ሰዎች መሞታቸው የተገለጸ ሲሆን፤ ከነዚህም መካከል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የጤና ባለሙያዎች ናቸው።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦  APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0